colormap #003366#336699#3366CC#003399#000099#0000CC#000066#006666#006699#0099CC#0066CC#0033CC#0000FF#3333FF#333399#669999#009999#33CCCC#00CCFF#0099FF#0066FF#3366FF#3333CC#666699#339966#00CC99#00FFCC#00FFFF#33CCFF#3399FF#6699FF#6666FF#6600FF#6600CC#339933#00CC66#00FF99#66FFCC#66FFFF#66CCFF#99CCFF#9999FF#9966FF#9933FF#9900FF#006600#00CC00#00FF00#66FF99#99FFCC#CCFFFF#CCCCFF#CC99FF#CC66FF#CC33FF#CC00FF#9900CC#003300#009933#33CC33#66FF66#99FF99#CCFFCC#FFFFFF#FFCCFF#FF99FF#FF66FF#FF00FF#CC00CC#660066#336600#009900#66FF33#99FF66#CCFF99#FFFFCC#FFCCCC#FF99CC#FF66CC#FF33CC#CC0099#993399#333300#669900#99FF33#CCFF66#FFFF99#FFCC99#FF9999#FF6699#FF3399#CC3399#990099#666633#99CC00#CCFF33#FFFF66#FFCC66#FF9966#FF6666#FF0066#CC6699#993366#999966#CCCC00#FFFF00#FFCC00#FF9933#FF6600#FF5050#CC0066#660033#996633#CC9900#FF9900#CC6600#FF3300#FF0000#CC0000#990033#663300#996600#CC3300#993300#990000#800000#993333

የምህላ ጸሎት

የምህላ ጸሎት አብ ሆይ ማረን ሃሌ ሉያ ወልድ ሆይ ይቅር በለን ፤ ሃሌ ሉያ ፣ ይቅር ባይ መንፈስ ቅዱስ ሆይ በይቅርታህ አስበን (3 ጊዜ በል) ለአንተ ፍጹም ምስጋናን እናቀርባለን። ቸር ይቅር ባይ ሆይ ማረን፤ ኃጢአታችንንም አስተሥርይልን፤ የእግዚኣብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነን በነፍስ በሥጋም ጠብቀን ። አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይቅር በለን ። በቸርነትህ ብዛት በደላችንን ደምስስ ፤ ይቅርታህንም ላክልን ። ይቅርታ ካንተ ዘንድ ነውና ፤ ሃሌ ሉያ ይቅር ባይ አብ ሆይ ማረን ። ይቅር በለን መሐሪ የሆንህ አቤቱ ይቅርታህን ስጠን ! የቀድሞ ኃጢአታችንንም አስባህ አታጥፋን ። በቸርነትህ አንተ ይቅር ባይ ነህና ፤ ለሚጠሩህ ለሚለምኑህ ሁሉ ይቅርታህ ብዙ ነው ። በእውነት ይጠሩሃል ፤ አንተም ዘወትር ትሰማለህ ፤ ሁሉን ለማድረግ የምትችል ነህ ሁሉን ለማድረግ የሚችል የአምላካችን ቃሉ እውነት ነውና ። ይቅርታውን ይልክልን ዘንድ አብን እንለምነው ፤ አብ ለለመነው ሁሉ ይበቃልና ሃሌ ሉያ ለርሱ ምስጋና ይገባል ሃሌ ሉያ ለርሱ ክብር ምስጋና ይገባል ። ሃሌ ሉያ ለሁሉ ጌታ ለክርስቶስ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ። ዛሬስ ተስፋዬ ማነው እግዚኣብሔር አይደለምን ? አቤቱ ነፍሴን ላንተ አደራ አስጠብቃለሁ ከምሕረት አምላክ ዘንድ ነፍሴን አደራ አስጠብቃለሁ፤ ከምስጋና አምላክ ዘንድ ነፍሴን አደራ አስጠብቃለሁ ። በጌታዬና በአምላኬ ነፍሴን አደራ አስጠብቃለሁ ከክፉ ሥራ ሁሉ ሰውነቴን(ነፍሴን ) አድናት ። ኑ እንለምነው እንለምነው እንማልደው የአምላካችን ቃሉ እውነት ነውና ። ሁሉን የሚችል የሚሳነውም የሌለ እርሱ ነው የድሆች አምላክ ተስፋ ላጡ ተስፋቸው የምትሆን አቤቱ! እኛ ወዳንተ ተማጥነናል (3 ጊዜ በል)

ከጧት እስከ ማታ እንደጠበቅኸን አቤቱ እንዲሁ ከማታ እስከ ጧት ጠብቀን (3 ጊዜ በል) እኛን ወገኖችህን አድነን ፣ የጥንት ተገዥዎችህንም ባርከን ፣ ስምህን ለምንጠራ ለኛ ለአገልጋዮችህ ድል መንሳትንና ኃይልን ስጠን ። የወገኖችህን ልጆች እኛን ጠብቀን በየጊዜውና በየሰዓቱ በመላእክት ታዳጊነት በውስጥ በአፍአ ጠብቀን ። በመስቀልህ ታዳጊነት እርዳን ። በመስቀልህ ተቤዤን ። ስለ ባለሟልህ ስለ አብርሃም ፤ ስለ ወዳጅህ ስለ ይስሐቅ ፣ ስለ መረጥከው ስለ እስራኤልም ብለህ አቤቱ ቃል ኪዳንህን አስብ ይቅርታህን ፈጥነህ ላክ የፈጠርኸን እኛን ማረን ። የወገኖችህንም ኃጢአት አስተሥርይ ፤ የእጅህን ፍጥረቶች እኛን ማረን ፤ አቤቱ አታጥፋን ፤ ይህ በአንተ ዘንድ አይደረግ በእናትህ በማርያም አማላጅነት ፣ በአጥማቂህ በዮሐንስና በቅዱሳንህም ሁሉ አማላጅነት ሁል ጊዜ በመስቀልህ ታዳጊነት እርዳን፤ አቤቱ በፊትህ አታሳፍረን። እመቤታችን ሆይ ወደኛ ተመልከቺ ፤ ለኛ ለልጆችሽ ለምኚልን ፤ ከችግርና ከኀዘን ሁሉ አድኝን ። አቤቱ ጌታችን ሆይ ቀን ከኛጋር ሌሊትም በመካከላችን ሁን አቤቱ አንተ ከኛ አትለይ ከኛ ጋራ ኑር፤ ረዳትም ሁነን ፣ አትተወን አትናቀንም የሰላም አምላክ ሆይ ተራዳን። (3 ጊዜ በል) እመቤታችን ሆይ እመቤታችን ሆይ ወደኛ ተመልከቺ ፤ የልጅሽም ሰላም በኛ ላይ አድሮ ይኑር ( 3 ጊዜ በል ) አቤቱ ክርስቶስ ማረን ። (3 ጊዜ በል)

የቤተ ክርስቲያን ጸሎት። አቤቱ ፈጣሪያችን ሆይ ፍቅርን አንድነትን ስጠን። አቤቱ ፈጣሪያችን ሆይ ፍቅርን አንድነትን ስጠን ። ንጉሣችን ክርስቶስ ሆይ ወንድሞቻችንን ይቅር በላቸው እኛንም ይቅር በለን ። ትእ. ከዚህ በኋላ የኪዳን ጸሎት ቅዱስ ተብሎ ለማታ ጸሎት የተሠሩት 3ቱ ኪዳናት ይባሉ ። ሕዝቡም ቆመው ይስሙ ተሠጥዎውንም ይቀበሉ ። ትእ. ከኪዳን በኋላ ሕዝቡ እንደቆመ የምህላውን ጸሎት በግራና በቀኝ ይበሉት። ትእ. ከዚህ በኋላ ሕዝቡ እንደቆሙ ጸሎተ ሃይማኖትን ይድገሙ ትእ. ጸሎተ ሃይማኖት ከተደገመ በኋላ ሕዝቡ ይቀመጡ ። ቁሱ በክርስቶስ ፍቅር ስለመጽናት ያለውን ቃለ ስብከት ወይም ሌላውን ስብከት ያስማቸው፤