ደጅ ጠናሁ ቆይቼ ኪዳነ ምህረትን ተጽናናሁኝ እረሳሁ ሀዘኔን የአምላክ እናት እመቤታችን ሞገስ ሆኝኝ ቀሪው ዘመኔን የመከራው ዘመን አለፈ እንደዋዛ አንቺን ተጠግቼ የዓለምዋን ቤዛ የልጅሽ ቸርነት የአንቺም ደግነት ባርያሽን ሰውረኝ ከአስጨናቂ ሞት እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ ሰላም ለኪ ልቤ በአንቺ ፀና ከፍ ከፍም አለ በጠላቶቼም ላይ አፌ ተናገረ በማዳንሽ ስራ ባርያሽ ደስ ብሎኛል የኃያላንን ቀስት ልጅሽ ሰብሮልኛል እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ ሰላም ለኪ ደጄ ባዶ ሲሆን ወዳጆቼም ሸሹ በመርገም ምክአቸው ሊለያዩኝ ሲሹ እሱ የሰጠኝን እርሱ ወሰደ አልኳቸው እመቤቴ አለችኝ ብላ አሳፈርኳቸው እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ ሰላም ለኪ