ወዳጄ ሆይ እነሆ ውብ ነሽ የታተመች ፈሳሽ እንከን የሌለሽ የተዘጋች መቅደስ ንጽሕት አዳራሽ ሕዝቅኤል ያየሽ የምሥራቋ በር ማንም ያልገባባት ከአምላክ በስተቀር የልዑል ማደሪያ አማናዊት መቅደስ ስለ ንጽሕናሽ ምስጋናን እናድርስ አዝ . . . ሁለቱንም የሆንሽ እናትና ድንግል ማኅደረ መለኮት ወላዲተ ቃል ያለ ዘርዓ ብእሲ በኅቱም ድንግልና አምላክን የወለድሽ ሐመልማለ ሲና አዝ . . . ምሥራቀ ምሥራቃት ድንግል ሆይ አንቺ ነሽ ጨረቃን የምትመስይ ፀሐይን የወለድሽ የማለዳ ብርሃን ለዓይን የምታሳሺ ጽዮን እናቴ ሆይ ከጎኔ አትሽሺ አዝ . . .