ኪዳነምሕረት ርኅሩኅ ተይ አታቁሚኝ ከበሩ የሲኦል አለንጋ መራራ ነዉ አሉ አንቺ አማልጅኝ እግዝእትነ ኩሉ ሰጊድ ሰላም /2/ ኃያል እንዲህ ነዉ ኃያል ቅዱስ ሚካኤል ኃያል የለበሰዉ ልብሱ የወርቅ ሐመልማል የታጠቀዉ ሰይፉ የእሳት ነበልባል ይህም ተጽፏል በቅዱስ ቃል ሰጊድ ሰላም/2/ ኃያል እንዲህ ነዉ ኃያል ቅዱስ ገብርኤል ኃያል ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን ያዳናቸዉ ቂርቆስ ኢየሉጣን ከእሳት ያወጣቸዉ የሚረዳን ፈጥኖ ደራሽ ቅዱስ ገብርኤል ነዉ /2/ ሰማዕት እንዲህ ነዉ ሰማዕት ቅዱሰ ጊዮርጊስ ሰማዕት ለወዳጆቹ ፈጥኖ ሲደርስ ጣላቶቹንም ሲደመስስ ጊዮርጊስ ዘልዳዉ ንጉሥ ሳድቅ እንዲህ ነዉ ሳድቅ ተክለ ሃይማኖት ሳድቅ በአንድ እግራቸዉ ቆመዉ ለሰባት ዓመት ጠላትን ድል ነሱ በጾምና በጸሎት /2/