እናመስግን አምላኝችንን እናመስግን ፈጣሪያችንን ለዚህ ያደረሰንን ጨለማውን ወስዶ ብርሃንን የሰጠን ምስጋና ለእርሱ ይሁን ለኃያሉ ንጉሣችን ዘመናትን በዘመናት ያፈራርቃል ስለ ሁሉ ሁሉ ያውቃል ሳንለምነው የወደድነውን ይሰጠናል ከፈቃዱ ይሰማናል ውዳሴውን አዘጋጁ ያለ እረፍት አዲስ ቅኔ ተቀኙለት አዲስ መዝሙር ዘምሩለት እንደ ወዳጁ እንደ ዳዊት ዝናማትን ይሰጠናል በጊዜያቱ ፍጥረቱንም ይመግባል በየዕለቱ ልፈት የለው ለመንግሥቱ አዝ . . . ስሙ ላቅ ኃያል ንጉሥ የሚሉለት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ መላእክቱ በሰማያት ምስጋናውን ያቀርባሉ ያለእረፍት የተቤዥኸን ፍጥረትህን ክብር ምስጋና ላንተ ይሁን አዝ . . .