አምላካችን መድኃኔዓለም ነው መመኪያችን መድኃኔዓለም ነው በእልልታ እናመስግነው በጨለማው መንደር ስንኖር ታሰረን ከጥፋት ረግረግ ዲያብሎስ ዘፍቆን በመስቀል ላይ ሆኖ ከሞት ያዳነን ምስጋና ይድረሰው መድኃኒታችን ከሞት ባሕር ወጣን በእርሱ ቸርነት በድለን የነበርን አገኘን ምሕረት በፍቅሩ አረጋጋን አደለን ሰላም የሰላም ባለቤት መድኃኔዓለም ራሱን ሰዋልን ለእኛ በደል ካሣ ገና ጠላት ሳለን ኃጢአት በዓለም ነግሣ ያንን የሞት ባሕር አሻግሮናልና ውለታው ግሩም ነው ይድረሰው ምስጋና