ዜና

Earlier
ኦርቶዶክሳዊ ያልሆኑት ሁሉ ነገራችን በውል እንዲረዱት የቀረበ ትሑት ማብራሪያ።  (ብርሃኑ  አድማስ አንለይ)ብዙዎች በቅንነት ድርድር ምን ችግር አለው? መንፈሳዊ ሰዎች እንዴት ይህን እንቢ ሊል ይችላል? መነጋገር ምንድን ነው ችግሩ? እነዚህ እና ተመሳሳይ አሳቦችን አለመቀበል እንዴት እነካለሁ የሚል የአለመደፈር ስሜት የሚመስላቸው ሰዎች እንዳሉ ከአንዳንድ አስተያየቶች መረዳት ችያለሁ። ስለዚህ ድርድርን መቀበል ለምን አስቸጋሪ እንደሆነ ለመረዳት ጉዳዩ ምን እንደሆነ ማስረዳት እፈልጋለሁ።ቤተ ክርስቲያናችን ተጥሷል ብላ ውግዘት ለመፈጸም ምክንያት የሆናት የትኞቹም ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚጠቀሙበት መንፈሳዊ [...]
Mon, Feb 06, 2023
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ብርሃኑ ወልደ ዮሐንስ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ በስልክ እንደገለጹት ፣ ዛሬ ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጠዋትወደ ምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት የጸጥታ አካላት በመምጣት የሀገረ ስብከቱን  ሠራተኞችን ከሥራ በማስወጣት ሀገረ ስብከቱን ግቢ  ከሠራተኞች ነጻ እንዳደረገው ገልጸዋል።ፖሊስ በአርሲ ነገሌ አራት የደብር አስተዳዳሪዎችን ሕገ ወጡን ቡድን ተቀበሉ በማለት ሲያስገድድ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን ነን በማለታቸው አራት አስተዳዳሪዎች ታስረዋል ብለዋል።በመንበረ ጵጵስናው አብያተክርስቲያናት በታጠቁ ኃይሎች [...]
Sun, Feb 05, 2023
የሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት የሕገ ወጡን ቡድን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አናስገባም በማለት ቅጽራቸውን ሲጠብቁ ቢውሉም ለሕገ ወጡ ቡድን ከለላ የሰጠው የጸጥታ ኃይል በንጹሃን ላይ እርምጃ መውሰዱ ይታወቃል።በዚህም ሰማዕትነትን የተቀበሉ ምእመናን እንዳሉ ሁሉ በርካቶች ከፍታኛ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሐዋሳ የተለያዩ ሆስፒታሎች ተወስደዋል።እስካሁን ባለን መረጃም በሐዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል 6፣ በያኔት ሆስፒታል፣ በአላቲዮን ሆስፒታል 8 ምእመናን ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ።የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ [...]
Sun, Feb 05, 2023
***********************ጥር ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም """"""""""""""""""""""""""አዲስአበባ -ኢትዮጵያ **************የመግለጫው ሙሉ ቃል እነሆ፦በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!ለሚመለከተው ሁሉእሁድ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሦስት ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት በተፈጸመው የሕግ ጥሰት 26 ኤጲስ ቆጶሳት በመሾማቸው፣ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ቋሚ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ላሉት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊቃነ ጳጳሳት አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፏል፡፡ጥሪ የተደረገላቸው አባቶችም በቅጽበት ደርሰው ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አድርገው [...]
Sun, Jan 29, 2023
የጂማ ኦርቶዶክሳውያን በዛሬው ዕለት ለዓመታት የለፉባትንና ቅዳሴ ቤቷ ይከበራል ተብሎ በተጠበቀው የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ሲጠብቁ ቢውሉም ከአባታቸው ጋር ሳይገናኙ ቀርተዋል። የጅማ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በስፍራው ስለማይገኙ ቆሞሳት ባርከው ቤተ ክርስቲያኗ ትመረቅ ቢባሉም ምዕመናኑና ማኅበረ ካህናቱ እሳቸው የደከሙበትን ቤተ ክርስቲያን በሌሉበት አናስመርቅም፤ ይህ የኛ ቀን ነው፤ በእግዚአብሔር ቀን አባታችን ባሉበት እናስመርቃለን፤ የሠራነው የእግዚአብሔርን ቤት ነው ለምን ተፈተንን አንልም ብለዋል።የቤተ ክርስቲያኑ ምርቃት ወደ ሌላ ቀን መዘዋወሩንም  [...]
Sat, Jan 28, 2023
ሥርዓተ ቀብራቸው፣ ነገ ረቡዕ ከጸሎተ ቅዳሴ በኋላ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፤ ወደ ዩኒቨርሲቲ ያደገውን አንጋፋውን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ለ20 ዓመታት መርተዋል፤ ዐሥራ አራቱን ቅዳሴያት በመስኮብኛ(ሩሲያ ቋንቋ) ተርጉመዋል፤ ስንክሳርን በ800 ገጾች አትተዋል፤ የልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽንን ለ11 ዓመታት በበላይ ሓላፊነት መርተዋል፤ *** የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ጠባቂ ብፁዕ ዶክተር አቡነ ጢሞቴዎስ ዐረፉ፡፡ የ83 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የኾኑት አረጋዊው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ ትላንት መጋቢት 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ሌሊት፣ ከዚኽ ዓለም ድካም ማረፋቸውን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የሐዋሳ እና ጌዴኦ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ዜና ዕረፍት እንደተሰማ፣ የቋሚ ሲኖዶስ አባላት እና በቅርብ ያሉ ብፁዓን አባቶች፣ ዛሬ ጠዋት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት መወያየታቸውንና የብፁዕነታቸውን ሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓት አስመልክቶ ውሳኔዎችን ማሳለፋቸውን ብፁዕ ዋና ጸሐፊው ገልጸዋል፡፡ በዚኽም መሠረት፣ ዛሬ ማክሰኞ ከቀኑ በ11፡00፣ ቅዱሳን ፓትርያርኮች፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሓላፊዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት፣ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለብፁዕነታቸው ጸሎት ይደረጋል፡፡ ከዚኹ ጋራ ተያይዞ፣ ነገ ረቡዕ፣ መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ከረፋዱ በ4፡00 ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፤ ጸሎተ ቅዳሴውም እንዳበቃ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ለረጅም ጊዜ ባገለገሉበት በዚያው በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡ በመኾኑም፣ ቅዱሳን ፓትርያርኮች እና [...]
Tue, Apr 06, 2021
በአ/አበባ ሀ/ስብከት በስሟ የሚገኙ 38 ይዞታዎችን ያቀፈ ዕቅድ ነው፤ የሌሎች 40 ማክበሪያዎችን ይዞታ ለማረጋገጥ ምላሽ እየጠበቀች ነው፤ የጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ባለቤትነቷን የሚያረጋግጥ ካርታ ጠይቃለች፤ ከዕሴቷ ጋራ የማይቃረኑ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ዐቅዳለች፡፡ *** በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ጃንሜዳን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የበዓለ ጥምቀት ማክበሪያ ቦታዎችን ለማልማት ዕቅድ የነደፈች ሲኾን፣ የጃንሜዳ ባለቤትነቷን የሚያረጋግጥ  ካርታ እንዲሰጣት ጠይቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የካርታ እና የይዞታ ጉዳይን የሚከታተለው እና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጸዴቅ የሚመራው ኮሚቴ፣ ሰሞኑን  ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋራ ባደረገው ውይይት፣ ቤተ ክርስቲያን በስሟ የሚገኙ 38 የባሕረ ጥምቀት ቦታዎችን በተለያየ መልኩ የማልማት ዕቅድ እንዳላት ማስታወቁን፣ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመረጃ ክፍል ሓላፊ ላዕከ ሰላም ግርማ ተክሉ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የበዓለ ጥምቀት ማክበሪያዎች፣ በመንግሥትም በግል ባለሀብቶችም እየተቀነሱ በመወሰድ ላይ እንዳሉና ይኸውም ቦታዎቹ፣ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ለጥምቀት በዓል ማክበሪያነት አገልግለው ከዚያ በኋላ ሳይሠራባቸው መክረማቸውን በመመልከት እንደኾነ የሚጠቅሱት ላዕከ ሰላም ግርማ፣ ይህ ኹኔታ ያሳሰባት ቤተ ክርስቲያን፣ ቦታዎቹን የማልማት  ዕቅድ መንደፏን ገልጸዋል፡፡ በተለይ ቤተ ክርስቲያኒቱ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙት 78 ጠቅላላ የበዓለ ጥምቀት ማክበሪያዎች ውስጥ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በተረከበችባቸው 38ቱ የጥምቀት ማክበሪያ ቦታዎች ላይ፣ ከእምነቱ ዕሴት ጋራ የማይቃረኑ የማኅበራዊ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር መታቀዱን ነው ላዕከ ሰላም ግርማ ያስረዱት፡፡ በተቀሩትም ቦታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደተገኘባቸው ወደ ልማት እንዲገቡ አቅጣጫ መቀመጡን አመልክተዋል፡፡ በቦታዎቹ ላይ ሊተገበሩ ከታቀዱት [...]
Sun, Jan 17, 2021
ጃንሜዳን ለበዓለ ጥምቀት ዝግጁ የማድረግ ሥራ በይፋ ተጀምሯል፤ ጃንሜዳን ለበዓለ ጥምቀት ዝግጁ የማድረግ ሥራ፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ታኅሣሥ 8 ቀን 2013 ዓ.ም. ማለዳ 12:00 ሰዓት ላይ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክብርት ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ሓላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል። ቅዱስ ፓትርያርኩ በክንውኑ ላይ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፣ የከተማ አስተዳደሩ የጥምቀት በዓል ከመድረሱ በፊት ጃንሜዳን አጽድቶ ለማስረከብ በገባው ቃል መሠረት የገበያ መዋያውን በማንሣት እና በማጽዳት፣ ለበዓሉ ዝግጁ በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የይዞታ ባለቤትነቱን በማረጋገጥ ረገድም፣ የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። ክብርት ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፣ የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የከተማዋን ሕዝብ ከቫይረሱ ሥርጭት ለመታደግ ሲባል፣ የአትክልት ገበያው ወደ ጃንሜዳ መዘዋወሩ እና እስከ ዛሬ ድረስ አገልግሎት እየሰጠ መቆየቱን ጠቅሰው፣ የከተማ አስተዳደሩ ከጥምቀት በዓል አንድ ወር በፊት የአትክልት ገበያውን ከጃንሜዳ ሙሉ በሙሉ በማንሣት ቦታውን ለበዓሉ ዝግጁ የማድረግ ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ምክትል ከንቲባዋ አያይዘውም፣ በቀሪዎቹ ቀናት መሬቱን የመደልደል እና አረንጓዴ የማድረግ ሥራ፣ በከተማ አስተዳደሩ በኩል ተጠናከሮ እንደሚቀጥል አመልክተው፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ የተደራጁ ወጣቶችም የከተማ አስተዳዳሩ ከሚያከናውነው ሥራ ጎን በመቆም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ እምነታቸው ገልጸዋል። በቀጣይም፣ በጃንሜዳ ባለቤትነት በሚነሡ ጉዳዮች ዙሪያ፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋራ በመመካከር እና በመወያየት እንደሚሠሩ ተናግረዋል። አትክልት ተራ፣ በአኹኑ ሰዓት ከጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ሙሉ በሙሉ [...]
Thu, Dec 17, 2020
በዓሉ እንዳይከበር ከማስታጎል ጀምሮ የማክበሪያ ቦታዎችን መንጠቅ እየተለመደ መጥቷል፤ ከአዲስ አባባ 78 የበዓሉ ማክበሪያዎች፣ ይዞታቸው በሕግ የተረጋገጠላቸው 38ቱ ብቻ ናቸው፤ ለቀሪዎቹ 40 ማክበሪያዎች ካርታ እንዲሰጣት ቤተ ክርስቲያን ብትጠይቅም ምላሽ አላገኘችም፤ በያዝነው ዓመት ብቻ፣ በልዩ ልዩ ክፍላተ ከተማ ከ6 በላይ የማክበሪያ ይዞታዎች ተነጥቀዋል፤ ከ40 በላይ ገዳማት እና አድባራት የዘንድሮውን በዓለ ጥምቀት የሚያከብሩበት ቦታ የላቸውም፤ በልማት እና በስፖርት ማዘውተሪያ ሰበብ፣ መንጠቅ እና ምትክ አለመስጠት ተባብሶ ቀጥሏል፤ *** በማስተር ፕላኑ ታሳቢ ሳይደረጉ መንገድ የወጣባቸውና ጠፍ የኾኑ አብሕርተ ምጥምቃት አሉ፤ መንግሥት ዝንፈቱን በጊዜ አርሞ ካላስተካከለ፣ የቅርሱን ደረጃ እና ህልውና አስጊ ያደርገዋል፤ የቱሪስት መስሕብ የኾነውን ሳይጠብቁ ተመራጭ እና ቀዳሚ መዳረሻ መኾን እንደምን ይቻላል? ክብርት ም/ል ከንቲባዋ፣የጃንሜዳን ጽዳት በማስጀመር ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና እናቀርባለን፤ ጃንሜዳን ጨምሮ የኹሉም ባሕረ ጥምቀት ይዞታዎቻችን ባለቤትነት በሕጋዊ ካርታ ይረጋገጥ፤ ይዞታዎቹን መዳፈር የዓለም ቅርስ በዓለ ጥምቀት የማንም ቅርስ እንዳይኾን ማድረግ ነው! *** የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዐደባባይ ከምታከብራቸው ዐበይት በዓላት አንዱ፣ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት በዓል ነው። በየዓመቱ ጥር 10 ቀን ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው፣ በካህናት ሃሌታ እና በምእመናን እልልታ ታጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት ወርደው በጊዜያዊነት በዚያው ዓርፈው፣ ደማቅ እና ማራኪ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት የሚፈጸምበት፣ ልዩ እና ተናፋቂ ማኅበራዊ መስተጋብሮች የሚከናወኑበት ጥንታዊ እና ታሪካዊ በዓል ነው – በዓለ ጥምቀት፡፡ ከ1500 ዓመታት በላይ ሳይቋረጥ የተከበረው እና በመከበር ላይ ያለው፣ በአገራዊ ዕሴትነቱ እና የውጪ ጉብኝዎችን በመሳብ ወደር የማይገኝለት ሕብራዊው የጥምቀት – ከተራ ሥነ በዓል፣ የኢትዮጵያውያንና የመላው ዓለም የማይዳሰስ [...]
Mon, Dec 14, 2020
• “የማውቀውን እናገራለኹ” በሚል ርእስ የሰነዱት ግለ ታሪካቸው ለስርጭት ተዘጋጅቷል፤ • በነገረ መለኰት የማስተርስ እና የፒኤችዲ ዲግሪዎች የሞስኮ እና የፕሪስተን ምሩቅ ነበሩ፤ • ሥርዓተ ቀብራቸው፣ ነገ እሑድ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፤ *** የሲዳማ ጌዲዮ እና ቡርጂ ዞኖች አህጉረ ስብከትን በሊቀ ጳጳስነት ያገለገሉት ብፁዕ ዶክተር አቡነ ገብርኤል ዓረፉ፡፡ ብፁዕነታቸው፣ ባለፈው ጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ፣ ከእርግና እና ሕመም ጋራ በተያያዘ ከሓላፊነታቸው ተገልለው ረዳት እንዲመድብላቸው መወሰኑ የሚታወስ ሲኾን፣ ዛሬ ቀትር ገደማ በመንበረ ፓትርያርኩ መኖሪያቸው በተወለዱ በ80 ዓመት ዕድሜአቸው ዓርፈዋል፡፡ የብፁዕነታቸው የሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓት በቋሚ ሲኖዶስ የሚወሰን ሲኾን፣ ነገ እሑድ ሰንበት፣ ኅዳር 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቅዳሴ ውጪ፣ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ተጠቁሟል፡፡ ከካህን አባታቸው ከመምህር ገብረ ሕይወት እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብርነሽ፣ በወሎ ክፍለ ሀገር በዋግ አውራጃ በ1933 ዓ.ም. የተወለዱት ብፁዕነታቸው፣ የወሎ ክፍለ ሀገር ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ብፁዕ አቡነ ይሥሓቅ ማዕርገ ዲቁናን፤ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከቆሞስ ሊቀ ምርፋቅ ኤርሚያስ ሥርዓተ ምንኵስናን በ1958 ዓ.ም.፤ ሥልጣነ ቅስናን ከወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በ1959 ዓ.ም. ተቀብለዋል፡፡ የቅኔንና የአገባብን ይትበሃል በሚገባ አጠናቀው በመምህርነት የተመረቁት፣ የአቋቋም እና የትርጓሜ መጻሕፍት ዐዋቂው ብፁዕ አቡነ ገብርኤል፣ በ1962 ዓ.ም. ወደ ቀድሞዋ ሶቭየት ኅብረት ተልከው ከሌኒን ግራድ መንፈሳዊ ኮሌጅ የማስተር ኦቭ ዲቪኒቲ ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ውጤት አግኝተዋል፡፡ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በዚኹ መንፈሳዊ ኮሌጅ ቀጥለውና በሚገባ ፈጽመው በትምህርተ ሥጋዌ(ክሪስቶሎጂ) ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል፡፡ ወደ ሰሜን አሜሪካ [...]
Sat, Dec 05, 2020